top of page
  • Writer's pictureየመስቃን ብዙሃን መገናኛ አውታረ መረብ

የሼህ ሁሴን ጅብሪል ትንቢታዊ ግጥሞች (ክፍል - 02)



የሼህ ሁሴን ጅብሪል ትንቢታዊ ግጥሞች (ክፍል - 02)

7. መናውን ፈሰርነው አንተ ሳትናገር

ድቤውም ዋሽንቱም መሰንቆው ጭራ አይቀር

ጠጅና ጉማሬ ጫት ስንቅም እንደምር

ጀባ ብለንሃል በዟሂር መነጸር

ሐሲድ የሚመታ አንድ እንኩዋን ሹም ሳይቀር::

8. አላህ ካደረገን የኸልቁ ወዳጅ

በድቤና በጫት ልጀምር በጠጅ::

መሰንቆ እየመታሁ ልወዝወዘው እንጅ

በጭራ በዋሽንት ሰው ባልነካው እጅ

አውሊያ እምጠራበት ሶላት ሳልሰለች::

9. ጫት ባፋችን ይዘን ጠጅ እየጠጣን

ጥቁር ጭራ ይዘን ድቤ እየመታን

ሐሲድ እንዳይነካን አውሊያ እየጠራን

አምስት አውቃት ሶላት እየሰጋገድን

ሰው ያልነካው እቃ ጀሊሉ ሰጠን::

10. መጪውን አየነው ጉድ አጃኢበት

ዓለም ስትስቅብኝ እኔ ሳቅኩባት

ለአዳም መህሉቃት ከወንድም ከሴት

ካለቁት በስተቀር ያሉት በሐያት

ተከትቦ አየዋለሁ ስሙን ወደፊት::

11. ስሙን ይነግረኛል ዋሪዳው ሳይስት

ገና በእናቱ ሆድ ሳኸለቅ ፊት

ለወልይ ለንጉሥ፣ ለራስ መሳፍንት

ምን አስለፈለፈኝ ሊታይ ወደፊት

እኔም በል ብሎኝ ነው የምወሸክት::

12. ሃምሳ ዓመት ስናገር ሰምተው ጉድ እያሉ

እንደ ፍልፈል አፈር ሰው ሲፈለፍሉ

(ሰምተው እንዳልሰሙ አላየንም አሉ

እንደ ፍልፈል አፈር ሰው ሲፈለፍሉ)

እኛም ሰደድናቸው ከአፈር እንዲተሉ

ቀሩ እንደፈራነው ውሸታም እንዳይሉ::


31 views0 comments

Recent Posts

See All
bottom of page