top of page
  • Writer's pictureየመስቃን ብዙሃን መገናኛ አውታረ መረብ

ደራሲ ማን ነው? (አያልነህ ሙላቱ )

Updated: Jun 9, 2019



ደራሲ ማን ነው

አንተ ባለቅኔ! አንተ ልብ-ወለድ ወላጅ

ሥነጽሑፍን ከሕዝብ ገንጥሎ ተራማጅ::

ከመካከል ቁመህ ደረትህን አትንፋ

ወይ እሳቱን አንድድ ወይ እሳቱን አጥፋ…

ወይ ነፋሱን አግድ ወይ ነፋሱን ግፋ

ወይ ደመናን ጥረግ ወይ ደመናን አስፋ

ወይ ትንፋሽህን ዋጥ ወይም ትንፋሽ ትፋ::

ወይ ዐይንህን ግለጥ ወይ ዐይንህን ዝጋ

ወይ ጀሮህን ድፈን ወይ ጀሮህን አትጋ::

ወይ ታጠቅ ተፈሪ ወይም ታጠቅ ቁምጣ

ወይም ፀሐይ አግባ ወይም ፀሐይ አውጣ::

አልሚ-አጥፊ ተብለህ አብጅ ዘመድ ጓድ

ሁለት የወደደ አያገኝም አንድ::

ነፋስ አንከባሎም ወደ አንዱ አይጎልትህ

መጥፎና መልካሙን ሳይመርጥ ጭንቅላትህ::

ሥነጽሑፍ የሕዝብ ናት የሰፊው ሕዝብ ምርጫ

የላትም ጉራንጉር የግል መሸጎጫ

የልፍኝ ቤት መግቢያ… የጓሮ በር መውጫ::

እና! የምንለው የደራሲው ብዕሩ

ወይም ከሕዝብ ሆኖ ቀይ ይሁን መስመሩ::

ከሕዝቡ ደም ነክሮ ይጻፍ የሕዝብ ዋይታ

ወይም ከውሃው ጠቅሶ በውሃው ግጥም ይምታ::

ከሁለቱ መርጦ ባንደኛው ካልጣፈ

ለደሙም ለውሃውም ጠላት ነው የጦፈ::

ግን ከመኸል ቁሞ መንገዱን ከዘጋ

ኸንጥ ይግባ ተገፍቶ ምን አለው ከእኛ

አያልነህ ሙላቱ ‹‹ወይ አንቺ አገር›› (2004)


31 views0 comments

Recent Posts

See All
bottom of page