top of page
  • Writer's pictureየመስቃን ብዙሃን መገናኛ አውታረ መረብ

የሼህ ሁሴን ጅብሪል ትንቢታዊ ግጥሞች (ክፍል - 08)



የሼህ ሁሴን ጅብሪል ትንቢታዊ ግጥሞች (ክፍል - 08)

45 ቴዎድሮስ ለጋሥ ሰው ነው ቸርነት አያጣም

ዘሩም ደኅና ሰው ነው ቢገጥም አይወጋም

ማንም ያሞኘዋል ያሳዝናል በጣም

ለሰውም ደኅና ነው እስላምን አይጎዳም

እራቅ ይላል እንጅ የእስላም ዘር አያጣም::

ዮሐንስ ንፉግ ነው ሰው ቢበላ አይወድም

የሰው ያየ ጊዜ ያደርጋል ጉድምድም

ሆዱም ለብቻው ነው ሰው አያስቀርብም

ለጦር ግን ጀግና ነው ቢሄድ አይታክትም::

46. የጠንቋይ ውዴታ ፍቅር ይቅርብህ

ለአንተ ሲህር አያጣም ይኸው ነገርኩህ

ቢያጣ አርን አያጣም እንዳይጥልብህ

ስታልፍ እንድትረግጠው ሰው እንዲስድብህ

አሩ ይሸታል ብለው ሰው እንዳይቀርብህ::

47. አሥር ዓመት ብችል ሊያርዱኝ ተሰለፉ

ለካስ ለዚህ ነውይ እምቢ ያለኝ እንቅልፉ

ለአላህ ትቼው ነበር በዱኒያ እንዲያልፉ

እንግዲህ ዘላለም መሬትን ይቀፉ

በቶሎ ገላግለኝ ሰው እንዳያለፉ::

48. በእነ ቀለመወርቅ ነሱር ባላገኝ

በመምሬ ጉርሙ ነሱር ባላገኝ

በእነ አለቃ ሣህሉ ነሱር ባላገኝ

በእነ አለቃ ውብነህ ነሱር ባላገኝ

እኒህ ተዋርደው ነው ንጉሥ የፈራኝ::

49. በእለቃ ቀለመወርቅ ነሱር ባላገኝ

በእነ ይመር አደም ነሱርን ባላገኝ

በእነ አለቃ እዮብ ነሱር ባላገኝ

(በአውገረድ አለማሽ ነስሩን ባላገኝ)

ችለን ሰደድናቸው እንቅልፍ ቢነሱኝ::

50. ነግሬአቸው ነበር ፊት ሳልታመም

አሁንም አየሁት አላህ ሲፈርም

አፈሩን በጥብጦ በጥቁር ቀለም

ቃልቻ ይኸን ፈሥር እንዳትታመም

በቀር ትጓዛለህ አምተህ ሳትሰልም::

51. አላማጣን አልፈህ ማይጨው ትዘምታለህ

ነጭ አሥመራ መጥቶ አድዋ ትገጥማለህ

አድዋን እንዳያልፍ በጣም ትዋጋለህ

ጦርህ ግን ያልቃሉ ድል ግን ታደርጋለህ

በመከርኩህ ምክር ነጃ ትወጣለህ::

52. የሸዋረጋ እናት ሐለቴን ያውቃሉ

ሁሴን መጣ ሲባል ጋንዎን ያጥባሉ

ቄጠማ ጎዝጉዘው አዱርስ ያቀርባሉ

ደስ ደስ እያለዎት በጣም ይስቃሉ

መጋረጃ ጋርደው ቁጭ ብለው ያድራሉ::


30 views0 comments
bottom of page