top of page
  • Writer's pictureየመስቃን ብዙሃን መገናኛ አውታረ መረብ

የሼህ ሁሴን ጅብሪል ግጥሞች (ክፍል - 14)


105. ቋንቋቸው ተብታባ ዲናቸው እስላም ነው

አገራቸው ቆላ ልብሳቸው ግልድም ነው

ጦራቸው ክፉ ነው አፈር የሚያስቅም

እኒህ ለሐበሻ መርዝ ናቸው ሹ(ስ)ም?

ከኒህ ጋር መጣላት የለውም ጥቅም::


106. በአሥመራ ወያኔ ከመጣ ችግር

መጀመሪያ አሥመራ ትሆናለች ቀብር

አክሱም ትጠፋለች በአንድ ቀን ጀንበር

ግሼን ላሊበላ ትሆናለች ቀብር

ሁሉም ይሸፍታል ሴት እናኳን ሳይቀር::


107. ስንት እጃኢብ ያያል በዱኒያ የቆየ?

እኛ ባንደርስበት የልጅ ልጅ ጉድ አየ

ጥበብ እንዳይለምድ አሻቅቦ እያየ

የነጮችን ሥራ ብልግናን ገበየ

(አባቷም ዝም አለ ፈርጇን እያየ)::


108. የሳዳቶች ቀለብ ቀንበጥ ሳትረክስ

አላፊው ሳይቅማት ሳትበሰብስ

ትንባሆ ሳይቅማት ተሸጣ ሳትረክስ

ተው አታበላሻት ወንድሜ እየቃምክ አልቅስ

አላህ እንዲያለብስህ ሸማና ቀሚስ::


109. ይሰማኝ እንደሆን ፉቅራን ልምከረው

ለሴት ጫት መቃሙን መትፋቱን ይተው

መብራት አጥፉ እያለ ሰው እንዳያየው

እኔም ዝም አልልም ዲኑን ሲያረክሰው

እንኳን አላህ ጠልቶት ደስ አይልም ለሰው::


110. ብዙ ጉድ አየሁኝ መጅሊስ ተጠርቼ

ቱፍታ ልትመታ ጅስሟን ገልጣ አይቼ

ጸጉሯንና ጡቷን ሲይዟት አይቼ

እራቅ ብዬ ቃምኩኝ እንዳልነካት በእጄ

ሰው ነገረኛ ነው ሐሜቱን ፈርቼ::


111. ጠጅ ጠጣ ይለኛል ሲሩን ሳያውቀው

እኔ ለጠጣሁት ምን ቅናት ያዘው

አላህ ሲይስተው እንጅ ለሰው ብዬ አልተው

ንገሩት ቃልቻን ኋላ እንዳያመው

እንደ መምሬ ጉርሙ ሳላበላሸው::


112. አምስት ወቅት ሶላት ስገድ ብንለው

መርቅኛለሁ አለኝ እዩት ይህን ሰው

ጫቱን ዋጀብ አርጎ ዲኑን ሊያጠፋው

ጫቱን እየበላ ቢሰግድ ምነው?

እኔም ዝም አልልም ዲኑን ሲያረክሰው::


113. ሶላት ካልሰገደ አብሮኝ እንዳይቅም

ሐድራ ያበላሻል የለውም ጥቅም

አይሰግድም ከመባል ሞት አይሻልም

አላህ አይለቀውም እስከ ዘለዓላም

ነገሬ ካልገባው ይጠይቅ ዓሊም::


114. የመተማን ትተን የሐውሳን እናውጋ

ሦስት ቀን ጨልሞ በአራተኛው ነጋ

ለዕለት ታግሎ ነበር ሐውሳ እንዳይወጋ

ስሙ የታወቀ ትልቅ ባለጸጋ

ሳይያዝ ያመልጣል ሐውሳ ግን ተወጋ::


115. ነገሩ እማይገባ የተወላገደ

በአሥመራ በትግሬ ሄዶ እየነደደ

እንዴት ያለ እሳት ከሸዋ ነደደ

ቢያጠፉት እምቢ አለ እየተዛመደ::


116. አንበሳ እግሩን ታሞ ደም ሲያለቃቅስ

ማማው ምስጥ በልቶት ይሆናል ብስብስ

ወደቅ ወደቅ ይላል ወፉን ሊያጨርስ

የዚያን ቀን አሳማ ይሆናል ንጉሥ

ሺምጦ የሚበላ ሰው የሚያስለቅስ::

63 views0 comments

Recent Posts

See All
bottom of page