top of page
  • Writer's pictureየመስቃን ብዙሃን መገናኛ አውታረ መረብ

የሼህ ሁሴን ጅብሪል ግጥሞች (ክፍል - 16)


128. ዘመን ተበላሽቶ ወደቅ ወደቅ ሲል

ነጭ ከባሕር መጥቶ ይስላሉ ሲል

ተፈሪ የዚያን ቀን ይሆናል ትል

ሜዳ ላይ ይወድቃል ሳያገኝ ጅልል::


129. አላህን ሰደብኩት ማን አለው ጠበቃ

ምን ሥፍራ ኖሮት ነው ለራሱ የሚበቃ

በዱኒያ እንደሆነ ይበልጣል የእኔ ዕቃ

ቃልቻ ይመስክር አላህ ካለው ዕቃ::


137. አውራ በሬ ታርዶ አንበሳ ሲያለቅስ

ሐበሻ የዚያን ቀን ትሆናለች ኩስ

ሽታዋ የሚያስከፋ የምታስነጥስ

የዚያን ዕለት ይወድቃል እስላምና ቄስ

የዚያን ቀን ያስፈራል አገር እንዳይፈርስ::

138. እኛ አፈር በገባን በአንድ መቶ ዓመት

ተፈሪ ዓይኑን ታሞ ይገባል መሬት

ማር የላሰ ሁሉ ይቀምሳል እሬት

የበላውም አይቀር ሽቅብ ሲያስተፉት

ካለው ይገድሉታል ለገዘብ ስስት::


139. ሸዋ እባቡን ሳይዝ ምስጢሩን በዝብዞ

ድርቡሽ አገር ገባ የሰውን ላብ ይዞ

እባብ ልቡ አይገኝ መጣ መርዙን ይዞ

ዓለሙ ላይ ተፋው ያገሩን ጅብ ሰዶ

አብሮ የሚበላ አንጀትን በዝብዞ::


140. ሷሊህና ቃሲም አብደላህና ዙበኗር

በወልቃይት ብቅ አሉ ትግሬ ሲበረበር

ኩታበር ገራዶ ትሆናለች ጠጠር

ጎጃም ትጠፋለች ሳትውል ሳታድር

ብዙ ሰው ይጠፋል ያውም ከባላገር::


141. አሥመራ ተወግቶ ወልቃይት መርዙን ተፋ

ሽሬና መቀሌ ይሆናል የከፋ

እንቅልፍ እንዳይወስድህ እርብ ሳይጠፋ

ይመስላል ላየው ሰው ቂያማ የተደፋ

እርብ ስንቱን ጣለው ጠብቆ ወረፋ::


142. ጋይንት ንፋስ መውጫ ድራና ፎገራ

እርብ ላይ ሞልቶ ሲዘፍን ሲያጎራ

ነጋዴው ይጮሃል መቀሌና አሥመራ

ምን ይበጀው ይሆን ጅልጋና ፎገራ?

ሸዋ ደፈረሰ እህሊን ሳይዘራ::


143. መግዛቱን ይገዛል የዮሐንስ ዘር

ወዲያው ለጥቂት ቀን ይላል ፈንጨርጨር

ተፈሪን ጥላ አርጎ ሲያሳድድ ሲቀብር

ቢያዝ ደግ ነበር አገሩን ሳይቀብር

በቀር ሸዋ አይረጋም አትጠራጠር::


144. ሐበሻ ተፈሪን ይዘው ከቀበሩ

አሥመራ በሞላ ይታጠራል በሩ

መቼም ላስተዋለው ብዙ ነው ነገሩ

እኔ እገሌ አልልም ብዙ ነው ምሥጢሩ

በጫካ አካባቢ መች ቀረ ነገሩ::

38 views0 comments

Recent Posts

See All
bottom of page