top of page
  • Writer's pictureየመስቃን ብዙሃን መገናኛ አውታረ መረብ

የሼህ ሁሴን ጅብሪል ግጥሞች (ክፍል - 19)


169. አሽሙር ነው ነገሬ እንዳትሳሳት

አፈር በገባን በአርባ አምስት ዓመት

በሐበሻ መሬት ይመጣል ፍጅት

አውሊያ የተባልክ በደኅና ሰንብት

ዚያራው ያስፈራል መኮች ባወሩት::


170. ወልይ የለም ካሉ የኸልቁን መብራት

መኮች ባወሩት መንገድ እንዳትሳሳት

ሽሊላ በላቸው ከወንድም ሴት

በዟሂር ከሞቱት በዱኒያም ካሉት::


171. አለህም እንዳልል ሥፍራህን ማን ያውቃል?

የለህም እንዳልል ሥፍራህን ማን ያውቃል?

እንዴት የአንተን ሥፍራ ሸይጧን ይደፍረዋል?

ወትሮ ጭቡ ሱሪ ሰው ያስወነጅልሃል

ያልሆነውን ሆነ እያለ ያወራል::


172. ከአሜሪካ ወዲያ አለ ጥሩ ባሕር

ሃያ አምስት ያስኬዳል በግምት በእግር

ከዚያ አንድ ጎራ አለ ተተክሎ እንደ ጦር

ነጮች ከዚያች ሥፍራ ሳይደርሱም አይቀር

ላዩ ግን ሜዳ ነው የአንድ ጋሻ አገር::


173. ከአሜሪካ ወዲያ አለ ጥሩ አገር

ተራራውን ወጥቶ ከተገኘ ቀድ(ጽ)ር

ላዩ ግን ሜዳ ነው የሚያጭበረብር

ሥፍራው ከንዝ አያጣም ለሆነ ዘኪር

እዚህም አይደርሱ እንኳን ከቀመር::


174. ነጮች ሄዷል ካሉ ነጭን ከጨረቃ

መወሊድ የለም ካሉ ዚያራ ሰደቃ

ነቢን ከጠሏቸው የኸልቁን ጠበቃ

እንኳን ማውራት ቀርቶ መስማትም አይበቃ

ልባቸው እርኩስ ነው ሥራቸ ጨምላቃ::


175. አምስተኛው መዝሕብ ተሺጦ ሲለማ

ኋላ ጉድ ታያለህ የወሎ ኡለማ

የማታውቀው ነገር ቀርቧል ልትሰማ

ሰምተህ እንዳትከፍር ጆሮህ እየሰማ

አሟት እንዳይረግምህ አህያ ስትሰማ::


177. ምስክር የለኝ ተናግሬ አልሸሽ

አዋጁን ተከተል ሳትከፍር ብላሽ

በሁለት መንግሥት እንዳትቆሽሽ

ያሲን መስክሮታል ቁርዓንም አይዋሽ

ሌላ ካልፈሠሩት ሰው እንዲበላሽ::


178. በአምስትና በአራት በሦስት ሰጠር

ሲከትበው አየሁት ሼህ መሐመድ ኑር

ቆንጥሮ ያወራል መንደር ለመንደር

ጠቅላላ ሳይዘው ቀርቶ ሳይከርር

ሰውን እያየሁ ነው ጠልፎ ሲናገር::


179. ፈረስ ደኅና ሰንብት አላህ ይሁንህ

ነጭ ሐበሻ ገብቶ ጉድ አሸከመህ

የናታውቀው ነገር ጭኖ አስጎተተህ

ጉድክን ወደ ኋላ እንዳታይ ሆነህ

በአንዱ ስታለቅስ ሦስት ሰው ጫኑህ::

38 views0 comments

Recent Posts

See All
bottom of page