የመስቃን ብዙሃን መገናኛ አውታረ መረብ
Aug 27, 20181 min
የቀድሞ የኢትዮጵያ ሱማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አብዲ ኦማር መሐመድ በቁጥጥር ስር ዋሉ
ግለሰቡ አዲስ አበባ አትላስ ከሚገኛው መኖሪያ ቤታቸው ነው ዛሬ በፌደራል ፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋሉት፡፡
እንደ ፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ሕግ ገለጻ አቶ አብዲ በሕግ ጥላ ስር እንዲውሉ ካደረጋቸው የወንጀል ተግባራት መካከል የሰብአዊ መብት ጥሰት፣ የብሔር ግጭት፣ በሃይማኖት መካከል ግጭት እንዲፈጠር ማድረግ የሚሉት ተጠቅሰዋል፡፡
ፖሊስ እሳቸውን ጨምሮ በድርጊቱ ተሳትፈዋል የተባሉ ሌሎች አካላትን በቁጥጥር ስር እያዋለ መሆኑን ተዘግቧል፡፡
ምንጭ - EBC