የመስቃን ብዙሃን መገናኛ አውታረ መረብ
Oct 26, 20191 min
118. ተፈሪ ክፉ ነው ልቡም አይገኝ
ለሰው ይመስለዋል ይናገራል ቀኝ
ኋላ እንዲህ ሊዋረድ ፍዳውን ሊያገኝ
እሳት ሰደዱበት ዳግሚያ እንዳይገኝ
ዘላለም የማዝበርድ በደም የሚያዋኝ::
118. የተማረ ወድቆ ደንቆሮው ከገዛው
ማን አለብኝ ብሎ አገሩን ወረሰው
ጥሩ አርጎ ባለበት በገዛ እጁ ናደው
ምድር ሊቆረቁር ኋላ እንዲህ ሊቆጨው::
119. አላህ ዝም ብሎ መንግሥት ሊያሳስት
ሰው እንደፍሪዳ ሲታረድበት
ምን ይችል ሐበሻ ጉድ አጃኢበት
በጦሩ ጨፍጭፎ ላይረጋ መሬት
እንኳንም አልደረስን ስትነድ መሬት::
120. አሥመራ ልትጠፋ ገመዱ ሲላላ
በሸዋ ከተማ ይኸለቃል በላ
በሦስት ቀን ይያዛል ጎንደር ላሊበላ
አክሱም የዚያን ጊዜ ትሆናለች ሌላ
ማርያም ትጠፋለች አያዋጣም ብላ::
121. ምን ኑሮ ይገኛል መንግሥት ከከፋ
ሰውን ለመግደል ጦሩን ከአስፋፋ
ውሸት እንዳይመስልህ ይሆናል በይፋ
ጠብቀው ዘመኑን እንዳታንቀላፋ
ወቅታቸው እስኪቀርብ እስኪዘልቅ በይፋ::
122. አይጥ ጠብመንጃ ይዞ ከገባ ከዋሻ
ሳትታይ አትቀርም አሥመራ አላህ ቢሻ
በደም ተጨማልቋል ትሆናለች እርሻ
ብዙ ሰው ይጠፋል ሳይገኝ ወጌሻ
ክፉ ነፋስ ነፍሶ አልብሶት ቆሻሻ::
123. የአሥመራ ወያኔ ከያዘ ጠመንጃ
ደንግጦ ይሞታል የአሥመራ ስልቻ፣
የኋላ የኋላ ከቲማውን እንጃ
ምን አስለፈለፈኝ ላይገኝ ፈረጃ
ነስሩም አይታወቅ ዘላለም ጦር ብቻ::
124. የአሥመራ ጦርነት ታኅሣሥ ሲጀምር
ብዙ ሰው ይጠፋል ነገሩ ሳያምር
አይሰድም መስሏቸው ሸዋ ብዙ ጦር
ወዲያው ሰደዳቸው በሰማይ በምድር
ወያኔው ይሞታል አያገኝም ነስር::
125. ቀልባቸው ነጃሳ ስማቸው እስላም
ንጉሣቸው ሰወው ይበላል ጅም ላም
በስሙ የሚመራ ዓለም ለዓለም
ለዲን ተቆርቋሪ ለሁሉ የሚጠቅም
በኋላ ያልቃሉ ቀኑ ሲጨልም::
126. ባሕር ወዲያ ማዶ አራት ሰዎች አሉ
ከእነዚህ ሁለቱ በቀንድ ይበልጣሉ
የጌታችን መቃም አየነው ባይሉ
ለአዳም ፍጥረቶች በላዕ ይሆናሉ
በአመጡት በላዕ እነሱ ያልቃሉ::
127. ሐበሻ ሁለት ነጭ ሳይገቡም አይቀር
አንደኛው በፍቅር አንደኛው በጦር
አስበው ነበረ ሊያረጓት አገር
አምስት ዓመት ገዟት ሲል ደንገር ደንገር
እኩሉን በሥራ እኩሉን በጦር::