top of page
  • Writer's pictureየመስቃን ብዙሃን መገናኛ አውታረ መረብ

የሼህ ሁሴን ጅብሪል ግጥሞች (ክፍል - 15)


118. ተፈሪ ክፉ ነው ልቡም አይገኝ

ለሰው ይመስለዋል ይናገራል ቀኝ

ኋላ እንዲህ ሊዋረድ ፍዳውን ሊያገኝ

እሳት ሰደዱበት ዳግሚያ እንዳይገኝ

ዘላለም የማዝበርድ በደም የሚያዋኝ::


118. የተማረ ወድቆ ደንቆሮው ከገዛው

ማን አለብኝ ብሎ አገሩን ወረሰው

ጥሩ አርጎ ባለበት በገዛ እጁ ናደው

ምድር ሊቆረቁር ኋላ እንዲህ ሊቆጨው::


119. አላህ ዝም ብሎ መንግሥት ሊያሳስት

ሰው እንደፍሪዳ ሲታረድበት

ምን ይችል ሐበሻ ጉድ አጃኢበት

በጦሩ ጨፍጭፎ ላይረጋ መሬት

እንኳንም አልደረስን ስትነድ መሬት::


120. አሥመራ ልትጠፋ ገመዱ ሲላላ

በሸዋ ከተማ ይኸለቃል በላ

በሦስት ቀን ይያዛል ጎንደር ላሊበላ

አክሱም የዚያን ጊዜ ትሆናለች ሌላ

ማርያም ትጠፋለች አያዋጣም ብላ::


121. ምን ኑሮ ይገኛል መንግሥት ከከፋ

ሰውን ለመግደል ጦሩን ከአስፋፋ

ውሸት እንዳይመስልህ ይሆናል በይፋ

ጠብቀው ዘመኑን እንዳታንቀላፋ

ወቅታቸው እስኪቀርብ እስኪዘልቅ በይፋ::


122. አይጥ ጠብመንጃ ይዞ ከገባ ከዋሻ

ሳትታይ አትቀርም አሥመራ አላህ ቢሻ

በደም ተጨማልቋል ትሆናለች እርሻ

ብዙ ሰው ይጠፋል ሳይገኝ ወጌሻ

ክፉ ነፋስ ነፍሶ አልብሶት ቆሻሻ::


123. የአሥመራ ወያኔ ከያዘ ጠመንጃ

ደንግጦ ይሞታል የአሥመራ ስልቻ፣

የኋላ የኋላ ከቲማውን እንጃ

ምን አስለፈለፈኝ ላይገኝ ፈረጃ

ነስሩም አይታወቅ ዘላለም ጦር ብቻ::


124. የአሥመራ ጦርነት ታኅሣሥ ሲጀምር

ብዙ ሰው ይጠፋል ነገሩ ሳያምር

አይሰድም መስሏቸው ሸዋ ብዙ ጦር

ወዲያው ሰደዳቸው በሰማይ በምድር

ወያኔው ይሞታል አያገኝም ነስር::


125. ቀልባቸው ነጃሳ ስማቸው እስላም

ንጉሣቸው ሰወው ይበላል ጅም ላም

በስሙ የሚመራ ዓለም ለዓለም

ለዲን ተቆርቋሪ ለሁሉ የሚጠቅም

በኋላ ያልቃሉ ቀኑ ሲጨልም::


126. ባሕር ወዲያ ማዶ አራት ሰዎች አሉ

ከእነዚህ ሁለቱ በቀንድ ይበልጣሉ

የጌታችን መቃም አየነው ባይሉ

ለአዳም ፍጥረቶች በላዕ ይሆናሉ

በአመጡት በላዕ እነሱ ያልቃሉ::


127. ሐበሻ ሁለት ነጭ ሳይገቡም አይቀር

አንደኛው በፍቅር አንደኛው በጦር

አስበው ነበረ ሊያረጓት አገር

አምስት ዓመት ገዟት ሲል ደንገር ደንገር

እኩሉን በሥራ እኩሉን በጦር::

51 views0 comments

Recent Posts

See All
bottom of page