የመስቃን ብዙሃን መገናኛ አውታረ መረብ
Jan 25, 20201 min
145. ሐበሻ ስትደኸይ ስትቀጥን እንደ ድር
አዲስ መንግሥት ወጥቶ ይታደላል ምድር
ኸልቁ የዚያን ጊዜ ይለዋል ደንገርገር
ገንዘቡን ተወርሶ አታክልቱም ሳይቀር
እንኳን የተከለው የበረኻው ሳይቀር::
146. ይኸ ቻይና እሚሉት ዘራቸው ካልጠፋ
ችግር ይፈጠራል ይሆናል የከፋ
ማጥፋት ይሻል ነበር በአገር ሳይስፋፋ
ወልደን ሳንጥለው ልጃችን ሳይጠፋ
ጠብቀው ዘመኑን እስኪታይ በይፋ::
147. ሐበሻ ከገባ የቻይና ቁራሽ
ዲንን ያስፈራዋል እንዳይሆን ብላሽ
የዘመኑ ወጣት በሆኑት ቆስቋሽ
ስንቱን አደረጉት ደህይቶ እንዲሸሽ
እንዳይጣቀሙ ሀብታምና አራሽ::
148. ምን መላ ይገኛል ጦር ቢያከማቹት
አልገዛም ካለ ከወንድም ከሴት
ሸዋ ካልመከረ ይሆናል ወንፊት
እባብ መርዙን ከተፋ ይመጣል ፍጅት
ይህን እየሰማህ እንዳትገባ እሳት::
149. በድርቡሽ ሲገርመኝ የመተማ እልቂት
የማይጨው ሲገርመን የአድዋ ጦርነት
መቀሌን አየሁት አረሁ በልቶት
ሸዋ በገዛ እጁ በጫረው እሳት
ስንቱ ሰው ይነዳል ውቅሮ አዲግራት::
150. እንኳን የአንበሳ ልጅ እባብ ሲዞረው
ጀግና የሚወጣበት አገሩ የት ነው
ሥፍራውን ለይቼ እኔ ሳስታውቀው
ሽሬ ልጅ አንበራ ማይጨው ወያኔው
ምኒልክ ይመስክር ሲዋጋ ያየው::
151. የወልይ ልጅ ወልይ፣ የጀግና ጀግና ነው
እኛ እንኳን ባንቀምሰው በሌላው አየነው
በልተው እየጠጡ ጅስማቸው ቀጭን ነው
ወትሮም ደኅና ጎበዝ አካለ ቀጭን ነው
ተፈሪ የማይወፍር ሐሳብ በዝቶበት ነው::
152. ሸዋ አሥመራን ፈጅተህ አቃጥለህ በእሳት
ማምለጫም አታገኝ ሁሴን ፈረድኩት
ግን አሥመራ ያልቃል በራብ በጥማት::
153. ሐበሻ በሞላ በጦር ከተመራ
ወቅትቃቸው ያበቃል ፉቅራና ደብተራ
ለአገር ባይመቹ የሚሠሩት ሥራ
ምድር እያሳዩ ሲያስጥስ ደንቃራ
ጉዳቸው አያልቅም ቢወራ ቢወራ::
154. አሥመራ በጥጋብ ሲዘል ሲደነፋ
የልቡን ተናግሮ ገንዘቡን ሳያጠፋ
እስላም ከክርስቲያን ከሁሉም አይጠፋ
ሁሉም ሊከፋበት በረሃብ ሊያንቀላፋ
ወቅቱ ዘንበል ሲል ያለቅሳል በይፋ::
155. በርበሬ ቢጋገር እንጀራም አይሆን
አዟሪው ማን ይሆን አፍሳሹ ሊጡን?
አቡኪው ማን ይሆናል የሚሰድ እጁን
ሸዋ ግን አይፈራም ያውቀዋል ግዱን
በልቶ ሰው ያስባል እስኪገን አማን::
156. የከተማ ወንፊት በርበሬ እየነፋ
ንፋስ የመጣ እንደሁ ነፊው ዓይኑ ጠፋ
ዓይኑን እስከሚያሸው ነፊ አጥቶ ተደፋ
ንፋስ እያየ ነው በርበሬ የሚነፋ
ፍሬው ካልወደቀ ገለባ አይነፋ::