top of page
  • Writer's pictureየመስቃን ብዙሃን መገናኛ አውታረ መረብ

እሾክ ከስጋ ገብቶ (በሚፍታ ሸምሱ)


እሾክ ከስጋ ገብቶ (በሚፍታ ሸምሱ)

የወጋኝ እሾክ ፣ እንቢ አለ በመርፌ ፤

አልሆነም አምጡልኝ ፣ ልሞክር በወስፌ፤

ገላእሾክ ይዞ ፣ እንዴት ይረጋጋ ፤

ላውጣው እንጂ በግድ ፣ ከገባ ከሥጋ ።

ማንከሴም ቢሆን ለቀናት ብቻ ነው ፤

ከዘራ መያዙም ፣ ከቶ ምን ሊጎዳኝ ፣ ነገዬን ካሳመረው ። "

አቤት መመሰጥ ፣ ግጥሙ የኔ አይደለም

ባይሆን ለገጣሚው ፣ ይህ መልዕክቴ ይድረሰው ፤

ስጋህ ቢፈወስም ፣ ልብ ካልታከመ ፣ መች ይድናል ሰው ።

አሾሁን አውጥተህ ፣ ስጋህ ቢፈወስም ፤

ከማያላውስ ህመም ፣ ከጥላቻ አልዳነም ።

እሾሁ ሲወጋህ ፣ የቋጠርክባቸው ቂም ፤

የጎን ውጋት ሆኖ ፣ ከልብህ አልወጣም ።

ይቅር ተባብለህ ፣ የወጋህን እሾህ ፣ የወጋህ ካልነቀለው ፤

የልብ ህጥላቻ ፣ መልሶ ያስወጋሃል ፣ ትላንት የወጋህን ሰው።

ስለዚህ ወንድሜ ፣ ዜሮ ድምር አይሁን ፣ ስጋህም ልብህም፤

ይቅር በመባባል ፣ በምክክር ካልሆነ፣ በጭራሽ አይድንም።



50 views0 comments
bottom of page