top of page
  • Writer's pictureየመስቃን ብዙሃን መገናኛ አውታረ መረብ

የሼህ ሁሴን ጅብሪል ትንቢታዊ ግጥሞች



የሼህ ሁሴን ጅብሪል ትንቢታዊ ግጥሞች

1. ዋርዳው መጣና ቆይ አለኝ አንድ ዓመት

ጫትክን እየበላህ ሳታድር ከሴት

አምሬን እየሞላህ ጠጅን ሳታሸት

ደረሳህን ይዘህ ሳትወጣ ከቤት

እኔም ኸልዋ ገባሁ ቆየሁ አንድ ዓመት::

2. አንድ ዓመት ጫት ቅመን ዓለሙን ስንድር

ንጉሥ እየፈራኝ ሳይጠላኝ አሽከር

ወዲያው ስሜ ታውቆ ሸዋና ሐረር

እኔም በመስታወት ዓይኔን ሳሳምር

ቃሌ ሳይዛነፍ ሳልደናገር::

3. አላህ ሲያሳምረው ሰው እጣው ሲወጣ

ዓመት አስቀመጠኝ ከኸለዋ ሳልወጣ

ወዲያው መናም አየሁ አንበሳ ሲወጣ

ነብር እየመራኝ ጅብ ከፊቴ መጣ

ግመል ተሸክሞኝ የሆነ መላጣ::

4. መናቡ አይቼ ለሰው ሳላወራ

በሰባተኛው ቀን መጣ አንድ ቀብራራ

መሰንቆና ዋሽንት በእጁ ይዞ ጭራ

ከኔ ጋራ አደረ ጫት ሲቅም ሲያወራ

መሰንቆ እየመታ ሲዘፍን ሲያቅራራ::

5. አላህ ሲያሳድገው ነገሩ ሲሰላ

በስምንተኛው ቀን ጫት ስንቅም ስንበላ

ድቤ ተሸክሞ መጣ አንድ ሻንቅላ

ጫት በጨርቅ ይዞ ጠጅ በሸክላ

ሁሴን ቡን አፍላልኝ ነገሩ እንዲሰላ::

6. ስምንት ቀን ከደምኩ ሳትናገር አፌ

የቤቴን ግድግዳ ግንዱን ተደግፌ

ፊቴን እያጠብኩኝ እንዳይመጣ እንቅልፌ

እንዲቀመጡበት ጋቢዬን አንጥፌ

አይገርማችሁም ወይ ሳልነግድ ማትረፌ::

ጌቴ ገላዬ (ዶ/ር)


27 views0 comments

Recent Posts

See All
bottom of page