top of page
  • Writer's pictureየመስቃን ብዙሃን መገናኛ አውታረ መረብ

የሼህ ሁሴን ጅብሪል ትንቢታዊ ግጥሞች (ክፍል - 04)



የሼህ ሁሴን ጅብሪል ትንቢታዊ ግጥሞች (ክፍል - 04)

19. እመክርህ ነበረ መች እሺ ትላለህ

ሀሳብህ ብዙ ነው መንገድ ታበዛለህ

መተማ ለመዝመት አሁን ትሄዳለህ

(መመልስክን እንጃ እዛው ትቀራለህ)

በድርቡሽ ጎራዴ ራስህን ታጣለህ::

20. አንድ ዓመት ሲቀረው ምኒልክ ሊነግሥ

አላህ መተማ ላይ ይስላል መቀስ

በደም አጨማልቃ የምትቆራርስ

እራስ የምትቆርጥ ያውም የንጉሥ

አንደዜ ተመታች የማታላውስ::

21. አራት ወር ሲቀረው ምኒልክ ሊነግሥ

በመተማ በኩል ትጨሳች ጭስ

ጭሷ በራስ ገብታ (የምታስነጥስ) ትጨርሳለች ጭስ

እጅግም አትበጀው ለአጼ ዮሐንስ

አላህ ሽቶበታል አንገቱን ሊቀምስ::

22. እውቀትም የላቸው አሉን ጥንብ እርኩስ

ብለው ሰደቡን ደብተራና ቄስ

ሄጄ ልናገረው ለአጼ ዮሐንስ

ፈርጀለት ነበር መቅደላ ሲፈርስ

እንዴት የነቢ አሽከር ይሆናል እርኩስ?

23. የሰማም ያልሰማም ያልቅስ

መች እኔ እፈራለሁ ደብተራና ቄስ

መተማን ድል አድርጎ እሱ ቢመለስ

እንግዲህ የኔ ጫት ጥንብ ናት እርኩስ?

መተማ ካልሄደ እኔም ጫት አልቀምስ::


20 views0 comments

Recent Posts

See All
bottom of page