ሕይወት ማለቅ ቅኔ
ለእኔ ማለት የእኔ::
ወይም ሕይወት ሞፎ
የእኔነት ቀፎ::
በራሴ ውስጥ ያለ ያገር ፍቅር ወኔ
ባህል ኪነ ጥበብ ማህሌተ ቅኔ::
በመብላት … በማግሳት … ሕይወት ከታመነ
ጓዱ በዓለም የለም አካሉ ካልሆነ::
ካለዚያም መቀመጥ … መወዘፍ በሶፋ
ከሆነ የሕይወት እሷነት ይጥፋ::
ወይም እኔነቴ በእኔ ዘንድ አይኖርም
ወደ ኋላ አይሔድም … ወይ ወደላይ አይበርም
እሱም … እኔም … ግጥሜም ..
እንድንቆይ ባንድ ዕድሜ
እኔ ግጥም ልጻፍ … ታግሎ ይኑር ግጥሜ
ካሊያ ግን አልገፋም ኑሮን በዝም ትርጉም
ኑሮ እራሷ ትሁን የረከበች እርጉም
ሕይወት ከነምኗ . . .
ትበል እልም … ድርግም
አያልነህ ሙላቱ ‹‹ከድጡ ወደ ማጡ! የግዛተ -
ደርግ ግጥሞቼ ፲፱፻፷፰-፹፪›› (2004)