top of page
  • Writer's pictureየመስቃን ብዙሃን መገናኛ አውታረ መረብ

የሼህ ሁሴን ጅብሪል ትንቢታዊ ግጥሞች (ክፍል - 07)



የሼህ ሁሴን ጅብሪል ትንቢታዊ ግጥሞች (ክፍል - 07)

37. ድርቡሽ ጥሩ እስላም ልባቸው የጠራ

ሶላትን አይተውም ቢበዛበት ሥራ

ችግርም ቢገጥመው ይችላል መከራ

አገራቸው ሜዳ የለውም ተራራ

ልብሳቸው ቀሚስ ነው የለውም ዳኢም ታጥቀው ሥራ::

38. ከእኔ ተመርቀው ሴት ልጅ ከወለዱ

ለጉግሳ ይዳሯት እንዳትዛመዱ

ሌላም አያገባት ፈርዶታል ዘመዱ

እንግዲህ እሜቴ ጫት ቃሚን ይውደዱ

አሁን ነው መሸመት ደጎቹ ሳይሄዱ::

39. በአዳራሹ ገብተህ በእልፍኙ ላይ ውጣ

በእልፍኙ ላይ ገብተህ በአዳራሹ ውጣ

እንደምንም ብለህ ሸዋረጋን አምጣ

የተያዝክ እንደሆን እኔ በጉድ ልውጣ

እኔ ፈርጃለሁ ሌላ እንዳታመጣ::

ወንድ ትወልዳለች ግን የለውም ዕጣ::

40. በራስህ ገብቼ በሆድህ ብወጣ

ከትርንጎ በቀር ሌላ ምንም ታጣ

ይኸ ያልሆነ እንደሁ እኔ በጉድ ልውጣ

ሆድህን የሚገልጥ ሽማግሌ ይምጣ

ይኸንን ጉድ ሳላይ ከቤትም አልወጣ::

41. ተው አቶ ሙቀጫ እኔን አታላግጣ

ጌሾና ቡናህን ውጣና ቀጥቅጣ፣

በሽታም እንደሆንክ እኔ በጉድ ልውጣ

ማንን ታሞኛለህ እኔ አልወድም ላግጣ

እኔ እሳት አልገባም ነግረንሃል ቁርጣ::

42. ምኒልክ ክፉ ነው በስንቱ ፈተነኝ

እንድአለፉት ጠንቋይ በእሳት ሊያቃጥለኝ

በሰው እጅ አልጠፋም አላህ ካልገደለኝ

እንኳን ከመምሬ ፊት አላህ ሊቅ አረገኝ

እፈራው ነበረ በጅኑ እንዳይጠልፈኝ::

43. የምኒልክ ጠንቋይ ዋና ደብተራው

ያስፈጨው ነበረ ጅኑን እንደ ሰው

በርበሬ ነበረ የሚቋደሰው

ጅኑን እየላከ ስንቱን ሰው ፈጀው

መምሬ ሐሲድ ነው ከመጀመሪያው::

44. እንግዲህ ወንድሜ ስማኝ የኔን ፍርድ

መውለድህ አይቀርም ከጭን ከገረድ

ቁርኣን የሚቀራ ኢልምን የሚወድ

መጨረሻው ከፍሮ ካልሆነ ፈሳድ::


21 views0 comments

Recent Posts

See All
bottom of page